Welcome to
+
|
|
Help center
Home
Calender
Authentication & Equivalency
Survey
Announcement
Back
Announcement
News
Notice
Event
Online Admission
Back
Online Admission
Application Form
Registration Form
Resource
Back
Resource
Publication
Policy&Strategy
Educational Statics
Legal Document
Gallery
More
Support
Submit Ticket
My Tickets
Service
About
Contact Us
Status
Login
Announcement
በከተማ አስተዳደሩ በሚገኙ የመንግስት ቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ኮሌጆች የሰልጣኞች የክህሎት ውድድር ተካሄደ።
በከተማ አስተዳደሩ በሚገኙ የመንግስት ቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ኮሌጆች የሰልጣኞች የክህሎት ውድድር ተካሄደ።
05th April, 2025
በከተማ አስተዳደሩ በሚገኙ የመንግስት ቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ኮሌጆች የሰልጣኞች የክህሎት ውድድር ተካሄደ።
መጋቢት 24/2017 ዓ.ም
በአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ የ15ኛው ቴክኒክና ሙያ ሳምንት አንዱ አካል የሆነው 4ኛው ሀገር አቀፍ የክህሎት ውድድር "ብሩህ አዕምሮዎች ፤ በክህሎት የበቁ ዜጎች" በሚል መሪ ቃል በከተማዋ በሚገኙ ኮሌጆች በስድስት ክላስተር ተካሂዷል።
የክህሎት ውድድሩ ከዚህ ቀደም በኮሌጅ ደረጃ የተካሄደ ሲሆን በውድድሩ የተሻለ ውጤት ያስመወገቡ ሰልጣኞች ናቸው በዛሬው ዕለት በክላስተር ደረጃ በተካሄደው ውድድር የተሳተፉት።
ውድድሩን አስመልክቶ በኢንተርፕራይዝና ቴክኖሎጂ ልማት ዘርፍ የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን እና ኢንኩቤሽን አገልግሎት ዳይሬክተር አቶ ፀጋዬ በየነ በሰጡን መረጃ የክህሎት ውድድሩ በ19 የሙያ አይነቶች በ104 ሰልጣኞች መካከል እየተካሄደ ይገኛል ብለዋል።
የሀገሪቱን የቴክኖሎጂ ዕድገት በክህሎት በማዳበር እንዲሁም በጥቃቅንና አነስተኛ የተደራጁ ኢንተርፕራይዞችን በቴክኖሎጂ በመደገፍ የዘርፉን ዕድገት በማሳደግ ሂደት የክህሎት ውድድሩ ሚናው ጉልህ መሆኑንም አቶ ፀጋዬ ጠቁመዋል።
በክላስተር የተካሄደው የክህሎት ውድድር መጠናቀቁን ተከትሎ የውድድሩ አሸናፊዎች በቀጣይ ከተማ ደረጃ በሚካሄደው የክህሎት ውድድር እንደሚሳተፉ ይጠበቃል።
.