Welcome to
+
|
|
Help center
Home
Calender
Authentication & Equivalency
Survey
College
News
Office Head Message
More
Registration Guideline
User Manual
CoC Result
Login
College
በስራና ክህሎት ሚኒስቴር ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች የተመራ የድጋፋዊ ሱፐርቪዥን ቡድን በኮልፌ ቀራኒዮ ክ/ከተማ በሚገኙ የመንግስትና የግል የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ኮሌጆች የመስክ ምልከታ አካሔደ።
በስራና ክህሎት ሚኒስቴር ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች የተመራ የድጋፋዊ ሱፐርቪዥን ቡድን በኮልፌ ቀራኒዮ ክ/ከተማ በሚገኙ የመንግስትና የግል የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ኮሌጆች የመስክ ምልከታ አካሔደ።
31st May, 2025
በስራና ክህሎት ሚኒስቴር ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች የተመራ የድጋፋዊ ሱፐርቪዥን ቡድን በኮልፌ ቀራኒዮ ክ/ከተማ በሚገኙ የመንግስትና የግል የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ኮሌጆች የመስክ ምልከታ አካሔደ።
ግንቦት 22/2017 ዓ.ም
በፌዴራል የስራና ክህሎት ሚኒስቴር የአሠሪና ሠራተኛ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ዳንኤል ተሬሳ የተመራው የድጋፋዊ ሱፐርቪዥን ቡድን በክፍለ ከተማው አስተዳደር ኮልፌ ኢንደስትሪያል ኮሌጅ እና በግል ዘርፍ ተሰማርቶ በውጭ ሀገር ስራ የሚፈጠርላቸውን ዜጎች ማሰልጠኛ ሀይኒ የቤት አያያዝ ሙያ ማሰልጠኛ ማእከል በመገኘት የመስክ ምልከታውን አካሔዷል።
በድጋፋዊ መስክ ምልከታም የኮልፌ ኢንደስትሪ ኮሌጅ ያከናወናቸውን አፈፃፀሞችን የኮሌጁ ዋና ዲን ቢንያም አወቀ(ዶ/ር ) ገለፃ የተደረገ ሲሆን በሪፖርት መነሻነትም በኮሌጁ ምልከታ ተካሔዷል።
የድጋፋዊ ሱፐር ቪዥን ቡድኑ በተጨማሪ በግል ዘርፍ ተሰማርቶ በውጭ ሀገር ስራ የሚፈጠርላቸውን ዜጎች ማሰልጠኛ ሀይኒ የቤት አያያዝ ሙያ ማሰልጠኛ ማእከልን ከውጭ ሀገር የስራ ስምሪት ጋር በተያያዘ እየሰጠው የሚገኘውን ስልጠና አስመልክቶ ምልከታ አካሔዷል።
.