Welcome to
College የኢንኩቤሽን አገልግሎቱን በአዲሱ የዘርፉ እሳቤ ተቃኝቶ መተግበር እንደሚገባ ተገለፀ።

የኢንኩቤሽን አገልግሎቱን በአዲሱ የዘርፉ እሳቤ ተቃኝቶ መተግበር እንደሚገባ ተገለፀ።

22nd February, 2025

የኢንኩቤሽን አገልግሎቱን በአዲሱ የዘርፉ እሳቤ ተቃኝቶ መተግበር እንደሚገባ ተገለፀ።
የካቲት 14/2017 ዓ.ም
በአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ የኢንተርፕራይዝ እና ቴክኖሎጂ ልማት ዘርፍ የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን እና ኢንኩቤሽን አገልግሎት ዳይሬክቶሬት በኢንኩቤሽን አገልግሎት፤ በዞኒንግ እና ዲፈረሸንሼን ዙሪያ ለኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን ቴክኖሎጂ ሽግግር ምክትል ዲኖች እና አስተባባሪዎች ስልጠና በመስጠት ላይ ይገኛል።
ስልጠናውን በንግግር የከፈቱት በኢንተርፕራይዝ እና ቴክኖሎጂ ልማት ዘርፍ የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን እና ኢንኩቤሽን አገልግሎት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ጸጋዬ በየነ ስልጠናው በዘርፉ የሚሰጠውን የኢንኩቤሽን አገልግሎት በአዲሱ የዘርፉ እሳቤ ተቃኝቶ አዳዲስ የፈጠራ ሀሳቦችን በማከል ወደ ገበያ እንዲገቡ ያስችላል ብለዋል።
አሁን ላይ የኢንኩቤሽን አገልግሎቱ በተወሰኑ ኮሌጆች የተጀመረ መሆኑን ያስታወሱት ዳይሬክተሩ ስራው በሁሉም ኮሌጆች ተጠናክሮ እንዲቀጥል በማድረግ ሂደት ስልጠናው ጉልህ ሚና እንዳለው ጠቅሰዋል።
ዛሬን ጨምሮ ለተከታታይ ሁለት ቀናት በሚካሄደው ስልጠና በኢንኩቤሽን ምንነትና አተገባበር ከቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ኮሌጆች ነባራዊ ሁኔታ ጋር ባገናዘበ መልኩ ግንዛቤ እንደሚፈጠር እና የቀጣይ የትኩረት አቅጣጫ እንደሚቀመጥ ይጠበቃል።
.

Copyright © All rights reserved.