ዓለም አቀፉ የሴቶች ቀን በቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ኮሌጆች በድምቀት ተከበረ
የካቲት 30/2018 ዓ.ም
በአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ ዓለም አቀፉ የሴቶች ቀን (ማርች 8) በቢሮው ስር በሚገኙ የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ኮሌጆች የሚገኙ ሴት አመራሮችና ሰራተኞች በተገኙበት በታላቅ ድምቀት ተከብሯል።
በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ115ኛ ጊዜ በሀገራችን ደግሞ ለ50ኛ ጊዜ እየተከበረ የሚገኘው ይህ በዓል "50 ዓመት የሴቶች ድምጽ ለእኩልነት እና ለበለጸገች ኢትዮጵያ!" በሚል መሪ ቃል በተለያዩ ሁነቶች ተከብሯል።

.