ቢሮው ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር የስልጠና ክፍሎቹን በቴክኖሎጂ ማዘመን የሚያስችለውን የውል ስምምነት ፈፀመ።
🇪🇹ታህሳስ 21/2018 ዓ.ም🇪🇹
የስራና ክህሎት ቢሮ ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር በምርታማነት የልህቀት ማዕከል ውስጥ ለሚሠራው የስማርት ክፍሎች የኔትወርክና የዘመናዊ ቴክኖሎጂዎች ዝርጋታ ስራ በኢትዬ ቴሌኮም አማካኝነት እንዲሰራ የውል ስምምነት የፊርማ ስነስርአት አካሂዷል።
በፊርማ ስነስርዓቱ ላይ አሁለቱም ተቋማት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች እንዲሁም የልህቀት ማዕከሉ የማኔጅመንት አባላት ተገኝተዋል ። ስምምነቱ የልህቀት ማዕከሉን በማዘመን ረገድ ትልቅ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው ታምኖበታል።
.