Welcome to
+
|
|
Help center
Home
Calender
Authentication & Equivalency
Survey
Announcement
Back
Announcement
News
Notice
Event
Online Admission
Back
Online Admission
Application Form
Registration Form
Resource
Back
Resource
Publication
Policy&Strategy
Educational Statics
Legal Document
Gallery
More
Support
Submit Ticket
My Tickets
Service
About
Contact Us
Status
Login
Announcement
የአራዳ ማኑፋክቸሪንግ ኮሌጅ የ2017 በጀት ዓመት አፈጻጸምን ከአጠቃላይ የኮሌጁ ማህበረሰብ ጋር ገመገመ
የአራዳ ማኑፋክቸሪንግ ኮሌጅ የ2017 በጀት ዓመት አፈጻጸምን ከአጠቃላይ የኮሌጁ ማህበረሰብ ጋር ገመገመ
19th July, 2025
የአራዳ ማኑፋክቸሪንግ ኮሌጅ የ2017 በጀት ዓመት አፈጻጸምን ከአጠቃላይ የኮሌጁ ማህበረሰብ ጋር ገመገመ
የአራዳ ማኑፋክቸሪንግ ኮሌጅ የ2017 በጀት ዓመት አጠቃላይ የስራ አፈጻጸም ግምገማ ውይይት አካሂዷል። በዚሁ መድረክ ላይ ኮሌጁ በበጀት ዓመቱ የፈጸማቸውን በርካታ ተግባራት በመገምገም ለቀጣይ በጀት አመት የሥራ አፈጻጸም ትምህርት የወሰደበት መድረክ ፈጥሯል፡፡
በግምገማ መድረኩ ላይ የኮሌጁ ዋና ዲን ወ/ሮ ጌጤነሽ ዘርአብዛ እንደተናገሩት፣ ኮሌጁ ባለፈው በጀት ዓመት ያስቀመጣቸውን እቅዶች መሰረት በማድረግ በርካታ ስራዎችን የፈጸመ ሲሆን በቀጣይ በጀት ዓመት የመደበኛ ሰልጣኝ ቅበላ፣ የሪፎርም ስራዎች እንዲሁም በርካታ መደበኛና መደበኛ ያልሆኑ ስራዎች ላይ ትኩረት በመስጠት መፈጸም እንደሚገባ አመላክተዋል፡፡
በግምገማው ላይ የተሳተፉ አሰልጣኝና የአስተዳደር ሰራተኞች በበጀት ዓመቱ አፈጻጸም ላይ ጠንካራና ደካማ ጎኖችን አንስተው ሰፊ ውይይት ያደረጉ ሲሆን በቀረበው ሪፖርት መሠረት ያጋጠሙ ችግሮችና የተወሰዱ የመፍትሄ እርምጃዎች በማብራራት በቀጣይ ትኩረት ሊሰጣቸው በሚገቡ ጉዳዮች ላይ ሀሳብና አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።
በመጨረሻም የኮሌጁ ማህበረሰብ በቀረቡት ግብዓቶች ላይ ተመስርቶ የቀጣይ ዓመት እቅዱ አፈጻጸሙን ይበልጥ እንደሚያጠናክርና ለተፈጻሚነቱም በትጋት እንደሚሰራ አስታውቋል።
.