Welcome to
+
|
|
Help center
Home
Calender
Authentication & Equivalency
Survey
Announcement
Back
Announcement
News
Notice
Event
Online Admission
Back
Online Admission
Application Form
Registration Form
Resource
Back
Resource
Publication
Policy&Strategy
Educational Statics
Legal Document
Gallery
More
Support
Submit Ticket
My Tickets
Service
About
Contact Us
Status
Login
Announcement
የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ የ2017 ዓ ም የማዕከል፣ የክ/ከተሞች እና የቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች የግማሽ ዓመት የKPI ዕቅድ አፈፃፀም ምዘና ይፋ አደረገ።
የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ የ2017 ዓ ም የማዕከል፣ የክ/ከተሞች እና የቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች የግማሽ ዓመት የKPI ዕቅድ አፈፃፀም ምዘና ይፋ አደረገ።
05th April, 2025
የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ የ2017 ዓ ም የማዕከል፣ የክ/ከተሞች እና የቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች የግማሽ ዓመት የKPI ዕቅድ አፈፃፀም ምዘና ይፋ አደረገ።
መጋቢት 25/2017 ዓ.ም
በተያዘው የ2017 በጀት ዓመት ባለፉት ስድስት ወራት በተከናወነው KPI 9ዕቅድ አፈፃፀም ምዘና መሰረት በቢሮው ስር የሚገኙ የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ኮሌጆች እና ክፍለ ከተሞች ደረጃ ይፋ ሆኗል።
የከተማ
አስተዳደሩ እያከናወነ ላለው ክህሎት መር የስራ ዕድል ፈጠራ ተቋማቱ በቅንጅት በመስራታቸው በዘርፉ አበረታች ለውጥ እየተመዘገበ መሆኑን ያስታወሱት በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ስራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ ክቡር
#አቶ
ጥራቱ በየነ የተቋማቱን አፈፃፀም መሰረት ያደረገ ምዝና በማድረግና በደረጃ መፈረጅ የእርስ በእርስ ፉክክርን በማዳበር ለሻለ አፈፃፀም እንዲተጉ ያስችላል ብለዋል።
በዚህም መሰረት በKPI በተቀመጠው መመዘኛ መስፈርት ከክፍለ ከተሞች ሥራና ክህሎት ጽሕፈት ቤት አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ አንደኛ ደረጃ ላይ ሲቀመጥ ቂርቆስ እና አዲስ ከተማ ክፍለ ከተሞች እንደ ቅደም ተከተላቸው ሁለተኛና ሶስተኛ ደረጃ ይዘዋል።
በፖሊ ቴክኒክ ማሰልጠኛ ኮሌጆች በተካሄደው ምዘና መሰረት አቃቂ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ አንደኛ ደረጃ ላይ ሲቀመጥ ጄኔራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ እና ተግባረ ዕድ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጆች ሁለተኛና ሶስተኛ ደረጃ ይዘዋል።
በሌላ በኩል በኮሌጆች መካከል በተካሄደው ምዘና ኮልፌ እና የካ ኢንዱስትሪያል ኮሌጆችን በማስከተል ልደታ ማኑፋክቸሪንግ ኮሌጅ አንደኛ ደረጃን ይዟል።
በዛሬው ዕለት ይፋ ከተደረገው የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ኮሌጆች እና ክፍለ ከተሞች ደረጃ በተጨማሪ በሥራና ክህሎት ቢሮ የሚገኙ የአላማ ፈፃሚ ዳይሬክቶሬቶችና የአስተዳደር ክፍሎች ደረጃ ይፋ ተደርጓል።
.